Finote selam

THE 12THANNUAL TRIP OF FBIE TO FINOTE SELAM

JANUARY 17-26 2014.
Many people need help - old or young, man or women, religious or non-religious... We beleive that God is the ultimate answer for all problems but we also believe that there is a role we can play as human, as pofessionals, as Christians!

FBIE is taking a steps towards helping people suffering from sight related problems.

Dembi Dollo

The people who walked for years in darkness have seen a great light!(Isa 9.2)
 
Dembi Dollo Eye mission, October 2011.
Fighting Blindness In Ethiopia has been going back and forth to Ethiopia since 2006 and has given sight for over 1500 people. The team has been travelling all over the country East West North and South, giving eye treatments for the rural Ethiopian population who have not chance of getting this kind of eye treatments that they are receiving from FIBE.



Hosaina

Fighting Blindness In Ethiopia has made four trips to our ever needy country and treated those who live in a rural area of the land. 2006 was our first visit with a team of four doctors and three nurses to the town of Bahirdar. That was an experience of a life time for all the team. When we saw the number of patients who streemed into the centre every day we could not hide our emotion but cried. Even I as



Arba Minch

Arba Minch eye 2010
FightingBlindness in Ethiopia ARBA MINCH mission 2010
The 2010 Mission of fighting blindness in Ethiopia continued its annual programme further a field to southern the part of the country to the province of Gamu Goffa to Arba Minch town. Even though we did not hit our target in numbers it was a very successful mission.As always there were some problems on the way but we believed that what God want us to achieve for these poor people has been done.

አብረን እንሸከም

ዓይኔን አብራልኝ

የሕዝባችንን ችግር አብረን እንሸከም

ዓይን የሰውነት ብርሃን ናት!
ክብር ለእግዚአብሔር ይሁንና በቅርብ በተደረገው የሕዝብ ምዝገባና ኢስታትሰትክስ በተጨማሪም ከኢንተርናሸናል ኢስታትሰትክስ መረጃዎች እንደምንረዳው የሕዝባችን ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መጥቶ በቅርቡ ከ80 ሚሊዮን በላይ እንደሚሆን ይገመታል። ይህን ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር ስንመለከተው በረከት ነው። ‚ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት ግዙአትም ‚(ዘፍ 1.28)። ጌታ ከባረከንና ካበዛን ፤ ጤንነታችንን ጠብቀንና ተረዳድተን የመኖር ኃሊፊነት ደግሞ የኃሁላችን ተግባር መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ።

እግዚአብሔር በዓለም ሁሉ ተበትነን እንድንኖርም ያደረገበት የራሱ የሆነ አላማ አለው ብዬም አስባለሁ ።በተለይም እኛ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ተወልደን አዲስ ፍጥረት የሆንን ሁሉ፤ የተጠራነውና የተመረጥነው ለተለየ ዓላማ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ። ነገር ግን መጠራታችንና መመረጣችን ለራሳችን ብቻ እንደሆነ የምናስብ ከሆነ ዳግሞ የተጠራንበትን ዓላማና የጌታችንን ቃል በትክክል የተረዳን አይመስለኝም። ጌታ በወንጌል ውስጥ እንዲህ የሚል የትእዛዝ ቃል ትቶልናል፡፡ ‚ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህ በፍጹም አሳብህም ውደድ።...ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትል ናት‛ (ማቴ 22.37-40)። በበኩሌ በዚህ ትእዛዝ መሠረት መውደድ ያለብኝ ሰውን ሁሉ ነው። ለሕዝቤ ደግሞ ድርብ ኃላፊነት የተሰጠኝ ይመስለኛል። እርስዎም ኢትዮጵያዊ ከሆኑ ለሕዝባችን ጤንነትና ብልጽግና ኃላፊነት አለብዎት ብዬ አምናለሁ።
በዚህ መሠረታዊ ነገር ላይ ከተስማማን ‘የሕዝባችንን ችግር አብረን እንሸከም’ ወደ ተባለው ፍሬ ነገር ልመለስና እንዴት ለመርዳት እንችላለን? ብለን ካሰብን መንገዱ ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን አንዱን መንገድ በምሳሌ ልጠቁምዎት። ከባሕር ውስጥ እየተተፉ ውሀ አጥተው የሚሞቱ ብዙ አሶች እና በባሕሩ ወደብ ዙሪያ ለመሞት የቀረቡ ከብዙ ሺህ ባላይ የሚሆኑትን ያየ አንድ ወጣት አሶቹን ወደ ባሕር መልሶ መወርወር ጀመረ ይባላል። ታዲያ አንድ ሌላ ሰው አየውና ‘ኧረ አንተ ልጅ ለምን ትደክማለህ እነዚህን ሁሉ መልሰህ ልታድን ነው?’ ብሎ ሲጠይቀው፣ የልጁ መልስ ግን ልብ የሚነካ ነበር። ‚ኧረ አይደለም ፤ ነገር ግን የመለስኳቸው ሁሉ በሕይወት ይኖራለሉ አለው ይባላል።
መላውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመርዳት ባንችልም ፤ የምንችለውን ያህል ብናደርግላቸው የተረዱት ሁሉ ራሳቸውን ለመርዳት ይችላሉ። በሞራ የዓይን በሽታ ተይዘው አርሰው ለማምረት ያልቻሉትን ገበሬዎች እና ጋግረው ለመብላት ያልቻሉትን እናቶች ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ራእይ አለን። ይሀ ራእይ ‚Fighting Blindness In Ethiopia‛ ፋይትንግ ብላይንድነስ ኢን ኢትዮጵያ ከተጀመረ አምስት ዓመት ሆኖታል። በዚህ ጊዜ ውስጥ በጐጃም ፤ በወለጋ ፤ በሲዳሞ እና በገሙ ጐፋ ክፍላተ ሀገራት በመሄድ በሞራ የዓይን በሽታ ለታወሩት በገጠር ለሚኖሩ ወገኖቻችን የዓይን ቀዶ ጥገና በማድረግና ጨለማቸውን ወደ ብርሃን በመለወጥ 1083 በሽተኞችን አክሟል።
ለወደፊትም ሀገሪቱን በመዞር ይህንን እርዳታ ለማድረግ እቅድ አለን። የጌታ ፈቃድ ከሆነ በመጭው ጥቅምት ወር ወደ ደምቢ ዶሎ ፤ በጥር ወር ደግሞ ወደ ወልቅጤ ለመሄድና ተመሳሳይ ሥራ ለማከናወን እቅድ አለን። ይህን ሁሉ ለማድረግ ገንዘብ ፤ የሰው ጉልበትና ብዙ የሕክምና መሣሪያዎች ያስፈልጉናል። ስለሆነም የሕዝባችን ችግር ከተሰማዎትና ለመርዳት ካሰቡ ወይም አስተያየትና ምክር መስጠት ቢፈልጉ ፤ በዚህ ዌብሳይትና አዴራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።
ጌታ ኢየሱስ በነገር ሁሉ ይባርክዎት

Nekemte and Bahirdar

Nekemte and Bahir Dar Mission 2006-2008
 
Fighting blindness in Ethiopia was started in 2006 by a group of voluntary ophthalmic doctors and nurses. With the coordination of some eye clinics in the country we managed to get patients screened before the team arrived on site. The first mission was to northwest of the country called Bahirdar.